እንደ የቋንቋና የታሪክ አጥኚዎች እምነት የግዕዝ ቋንቋ ፊደላት ከካዕብ እስከ ሳብዕ እና እንደአስፈላጊነቱ ከዚያም በላይ ሆሄያት የተቀረጹት ከአራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን በኋላ ነው ብለው ለማሳመን ይጣጣራሉ፡፡ በማስረጃነትም በዐፄ ኢዛና ዘመነ መንግሥት ከ፫፻፳ወ፬-፫፻፴ወ፮ ዓ.ም. የነበረ ንጉሥ የመገበያያ የወርቅ ሳንቲም ላይ “ኢዛና ንጉሠ አክሱም” ተብሎ ለመጻፍ ተፈልጐ “አዘነ ነገሠ አከሰመ” ተብሎ የተጻፈበት ሳንቲም አግኝተናል ይላሉ፡፡ ይህ ሁሉ [...]
↧