“ዋ…!ድምፄ ባከነ” ብዬ አምርሬ ልበሳጭ ዳድቶኝ ነበር፡፡ ደግነቱ ግን የኢትዮጵያ ህዝብ ለተረቱ ታማኝ ነው፡፡ “ከማያውቁት መልአክ የሚያውቁት ሰይጣን ይሻላል” ብሎ የሚያውቀውን ይመርጣል፡፡ ደግነቱ ግን የኢትዮጵያ ህዝብ ለተረቱ ታማኝ ነው፡፡ “የቆጡን አወርድ ብላ የብብቷን ጣለች” ብሎ የብብቱን ይመርጣል፡፡ ደግነቱ ግን የኢትዮጵያ ህዝብ ለተረቱ ታማኝ ነው፡፡ “በቅሎ ማሰሪያዋን በጠሰች፤ በራሷ ላይ አሳጠረች” ብሎ አሳሪውን ይመርጣል፡፡ ወትሮስ፤ ከማያውቁት [...]
↧