አንድ ብልጣብልጥ ባለተራ ፤ ከያኔ ነኝ የሚል ጽፎ በእሱ ቤት የማላውቅበት ፤ መከደሩን ለንብ ቀፎ በየሔደበት ያወራል ፤ ጸሐፊያንን ነቃቅፎ ጋዜጣ መጽሔት ድረ ገጽ ፤ ወደዛ! እያለ ተጸይፎ አታንብቡ አትስሟቸው ፤ ብሎ ያርቃል አንባቢ የጌቶቹ ጉድ እንዳይወጣ ፤ እንዳይገለጥ ሸባቢ እንዴት ምን ነካህ? ለሚሉት ፤ ተገርመው በጭፍን ትችቱ ችግር መኖሩ መች ጠፋን ? ይሄ ሀገር [...]
↧