ፊቱ አሸቦ መስሎ፣ እንደደነገጠ፣ ተጎልጉሎ ወጥቶ፣ ዓይኑ እንደፈጠጠ፣ ባንኮኒው ጋ ሄዶ፣ ቢራውን ጨበጠ። የሆነውን እንጃ! ሁኔታው ያስፈራል፣ እንባው በጉንጩ ላይ፣ አቋርጦ ይፈሳል አልቅሶ ሲበቃው፣ ውጪ እየሰለለ፤ ያየውን በውስጡ፣ እያሰላሰለ፣ ገድለው ሲጥሏቸው፣ በዓይኖቼ አየሁ አለ። ወደ ተናጋሪው፣ አፍጠን እያየን፤ እንደልማዳችን፣ ዝም ተባባልን። ሰውዬው ቀጠለ፣ ገድለው ሲጥሏቸው፣ በዓይኖቼ አየሁ አለ! ዘለው ያልጠገቡ፣ እህል የተራቡ፣ አገር የተቀሙ፣ ፍትሕ […]
↧